የጉለሌ ከተማ ምክር ቤት 13ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባዔ እያካሄደ ይገኛል :: በምክር ቤት አባላት ከተነሱ ጥያቄዎች መካከል፦
በጉባኤው የምክር ቤት የመራጭ ተመራጭና የቋሚ ኮሜቴ አባላቱ ከመረጣቸው ህዝብ ጋር ባደረጉት ውይይት ምላሽና ማብራሪያ ያስፈልጋቸዋል ተብለው የተነሱት ጥያቄዎች ዋና ዋናዎቹ ፡-
የወጣቶች የስራ ዕድል ተጠቃሚነት የመስሪያ ቦታዎች ከማስተላለፍ አንጻር
ከኑሮ ዉድነት ከማረጋጋት አንጻር የሸማቾች የፍጆታ ምርቶች በቂ አቅርቦት አለመኖር
ከመሠረተ ልማት ስራዎች የውሃና የመብራት መቆራረጥና መጥፋት በተመለከተ
የአገልግሎት አሰጣጥ የትራንስፖርት አቅርቦት ችግር
የሠላምና ፀጥታ ስራዎች የዘረፋና አዋኪ ድርጊቶች መቅረፍ
የመልካም አስተዳደር የህዝብ መጸዳጃ በቂ ግንባታ አለመኖር
የመንግስት ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥ በተመለከተ የሚሉ ጥያቄዎች በምክር ቤቱ አባላት የተነሱ ሲሆን ለጥያቆዎቹም በአቶ ወልዴ ወገሴ ምላሽ የሚሰጥ ይሆናል፡፡