የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት የ2ኛ ሩብ ዓመት የገጽ ለገጽ የእንጠያየቅ መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል ።
በመድረኩ ላይ በመገኘት መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ እንደተናገሩት በክፍለ ከተማው አገልግሎት አሰጣጥ ስርዓቱን ለማዘመንና የተገልጋይን እርካታ ለማረጋገጥ በትኩረት የተሰራበት እንደሆነ ገልጸው የእንጠያየቅ መድረኩ የህብረተሰቡን ጥያቄ ፊት ለፊት ከሃላፊው ጋር በመገናኘት እየመለስን እንገኛለን ብለዋል፡፡
ዋና ስራ አስፈጻሚው አክለውም ህብረተሰቡ የሚፈልገውን አገልግሎት በጥራትና በፍጥነት ተደራሽ የማድረግና ብልሹ አሰራሮችን የመዋጋት መንግስት ለሕዝቡ የገባው ቃል በመሆኑ ይህን ተግባር የክፍለ ከተማው አስተዳደር እንደ ቁልፍ አጀንዳ ይዞ እየሰራበት እንደሆነ ተናግረዋል ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ዘውዱ ከበደ በበኩላቸው የከተማው አስተዳደሩ የህብረተሰቡን አገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት በመስራት ላይ ይገኛል በተለይም የሪፎርም ስራዎችን በመስራት ለአገልግሎት ጥራት ቅድሚያ በመስጠት ላይ ነው የኮሙኒኬሽን ዘርፉ የተቋቋመበት ዓላማ ለማሳካት ጠንካራ የኮሙኒኬሽን ስርዓት በመዘርጋት የህብረተሰቡን በከተማዋ ልማትና መልካም አስተዳደር ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል ።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሰርካለም ተፈሪ በበኩላቸው መድረኩ ተገልጋዩ ማህበረሰብ በመጀመሪያ ሩብ በተለያዩ ጊዜያት ያነሳቸው የአገልግሎት አሰጣጥ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንዳገኙ የሚያውቅበትና በቀጣይም እድል የሚሰጥ ከመሆኑ ባሻገር የዘመነ አገልግሎት አሰጣጥ ለማስፈን የጎላ ፋይዳ እንደሚኖረው ገልጸዋል።